የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
ከተማችን አዲስ አበባን ሁሉም የሚለማባትና ለኑሮ የተመቸች ሞዴል ከተማ ለማድረግ በሚደረገው ከተማ አቀፍ ጥረት መኖሪያ ቤት የግድ ብቻ ሳይሆን የነዋሪዎች ህይወት መሻሻል፣ የህልሞች እና እድሎች መሳካት ሁሉ መሰረት መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ የልደታ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤትም ይህንን ቁልፍ የሆነ ሰው ልጆች ፍላጎትና የልማት መሰረት በክ/ከተማ ደረጃ ለመመለስ ተልዕኮ ተሰጥቶት እየሰራ ያለ ተቋም ነው፡፡ በክ/ከተማዋ ያለዉን ከፍተኛ የሆነ የመኖሪያ ቤት ፍላጎት ለማሟላት ጥራት ያለውና ወጪ ቆጣቢ ቤት በማስገንባት፣ በፍትሐዊነት እንዲተላለፍ በማድረግ፤ ቀልጣፋና ውጤታማ የቤት አስተዳደር ስርዓት በመዘርጋትና በመተግበር የክ/ከተማዋ ነዋሪዎችን ተጠቃሚነትን ማሳደግና በዚህም ህይወታቸው እንዲሻሻል፣ ህልማቸውን እንዲያሳኩና እድሎችን እንዲጠቀሙ የተልዕኳችን እምብርት አድርገን እየሰራን ነው፡፡
ከጊዜ ወደጊዜ እየጨመረ የመጣውን የመኖርያ ቤት ችግር በዘላቂነት ለመፍታትም የተለያዩ ስልቶችን ቀይሰን እየሰራን እንገኛለን፡፡ በቀጣይም ተቋማዊ ለውጥ በማድረግ አሰራሮችን በማዘመንና በቴክኖሎጂ የታገዘ አገልግሎት በመስጠት የተገልጋዮቻችንን ፍላጎት በተሻለ መልኩ ለመመለስ ዝግጁ መሆናችንን እንገልጸለን፡፡..... ተጨማሪ ያንብቡ
አቶ ገመቹ ጌታቸው , የልደታ ክ/ከተማ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ




